RSS

Monthly Archives: November 2013

ሕዝብ እና ወያኔ ወዲህና ወዲያ!!!

ይኸነው ዓለሙ

ህዳር 18 2013

ኢትዮጵያዊያን ረከስን፣ በዓለም ዙሪያ ማንም እንደፈለገ የሚዘግነን ሆንን፣ ራሳችንን ለመከላከል የማንችል፤ ስለ እኛም ቆሞ የሚከራከርንል ያጣን ምስኪን ሕዝቦች ሆንን። በሀገራችን ሳይቀር ያሰብነውን ለመከወን አቅም የሌለን፣ አቅጣጫ ጠቋሚ ኮምፓሳችንን የተነጠቅን፤ የጉዞ መቆጣጠሪያ መሪያችንን ያስረከብን ምስኪን ሕዝቦች። ባቅራቢያችን ባካባቢያችን የተፈጠረውን ለኛ ምቹ ያልሆነ ድርጊት ለመቆጣጠር መወያየትና መተባበር የተሳነን፤ ሽሽትን፣ ስደትን ሩጫን እንደ ብቸኛ አማራጭ የተቀበልን ምስኪን ሕዝቦች። በተለይ በፋሽስት ወያኔ ዘመን ረከሱ ሳይሆን ዋጋ አጡ መባል የሚገባን ምስኪን ሕዝቦች። ወያኔዎች ካንደኛው ችግር ወደ ሌላው፣ ከቀዳሚው መከራ ወደ ቀጣዩ እንደፈለጉ ሲያገለባብጡን ለምን ብለን መጠየቅ ያቃተን፤ እሽን ብቻ የተካንን ምስኪን ሕዝቦች። ፋሽስት ወያኔ ልጆቻችንን፣ ባለቤቶቻችንን፣ ወገኖቻችንን ባደባባይ በጠራራ ፀሐይ ዐይናችን እያየ በሕዝብ ፊት በጥይት ሲደፋቸው እያየን ”ሲያልፍ ያልፋል እስኪያልፍ ያለፋል” እያልን አንድም ቀን ሳይልፍልን እኛ ቀድመን በማለፍ ላይ የምንገኝ ምስኪን ሕዝቦች። ኢትየጵያኒዝም የተሰኘ የአሸናፊነት መንፈስ በቅኝ ግዛት ሲማቅቁ በነበሩ አፍሪካዊያን ወገኖቻችን፣ በላቲን አሜሪካና የሰሜን አሜሪካ ጥቁር ሕዝቦች ደም ውስጥ እንዲንተከተክ ምክንያት እንዳልነበርን፤ ዛሬ በፋሽስት ወያኔ ዘመን ግን ያንን መንፈስ የምንናፍቅ፣ እንዲያጋሩን የምንሻ አሳዛኝ ሕዝቦች ሆነናል። Read the rest of this entry »

 
Leave a comment

Posted by on November 18, 2013 in AMHARIC, ARTICLE

 

Tags: , , , ,

የረጋ ውሃ ትርፍ መሻገት ነው

ይኸነው አንተሁነኝ

ህዳር 09 2013

ማንኛውም ማሕበረሰብ በጋራ እንዲንቀሳቀስ እንዲተሳሰብና እንዲረዳዳ የሚያግዙትን ማሕበራዊ እሴቶች በዘገምተኛ የለውጥ ሂደት ይገነባል። እነዚህ የገነባቸው ማሕበራዊ እሴቶችም የማህበረሰቡን በህሪ ለማረቅ ያልተጻፉ ህጎች ሆነው ያገለግላሉ። በዚህ መሰረትም ምንም እንኳ ባሕል ሰፋ ያለ ስነ ሃሳብ ቢይዝም ማንኛውም የማሕበረሰቡ አባል ያካባቢውን ባሕል፣ ሃይማኖት፣ አፈ ታሪኮች፣ ወጎች፣ የሰርግና የለቅሶው ስርአቶች፣ አካባቢንና ሀገርን የማስጠበቅ የጀግንነት ትውፊቱንና ሌሎችንም ሁሉ መቼና እንዴት እንደተማራቸው ሳያውቅ ተክኖባቸው ይገኛል።

እነዚህ ያልተጻፉ ነገር ግን በማሕበረሰቡ ውስጥ ለዘመናት ጸንተው የቆሙት እሴቶቻችን መቼ መነሳትና መርዳት እንዳለብን፣ አንድ ነገር የትና እንዴት መከወን እንዳለበት፣ በግልም ሆነ እንደ ማሕበረሰብ መቼ ማዘን፣ ማልቀስ፣ መደሰት ወይም መቆጣት እንዳለብን ይነግሩናል። እርግጥ ነው እነዚህ እሴቶች እንደየማሕበረሰቡ የእድገት ደረጃ በመጠኑም ቢሆን እየተሞረዱና በሚመች መልኩ እየተስተካከሉ የሚቀጥሉ እንጅ ፈጽሞ የሚጠፉ አይደሉም። ስለሆነም ወንድሞቻችንን የሚያሳዝነው ካላሳዘነን፣ ወገኖቻችንን ያስቆጣው ካላስቆጣን  በውስጣችን አንዳች አደገኛ ነገር እየተከወነ መሆኑን ለመጠርጠር ብዙ መባዘን አያስፈልገንም። Read the rest of this entry »

 
Leave a comment

Posted by on November 9, 2013 in AMHARIC, ARTICLE

 

Tags: , , , , ,